የስርአተ ምግብ መፈጨት ላይ አደጋ የሚፈጥሩ ድርጊቶችን ማድረግ አይመከሩም፡፡
በዘልማድ ከምግብ በኋላ የሚደረጉ ድርጊቶች ብዙ ጊዜ ችግር ሲፈጥሩ ይስተዋላል፤ ከምግብ አለመፈጨት እስከ የጤና እክል።
እነዚህ ደግሞ ከምግብ በኋላ ባይደረጉ የሚመከሩ ናቸው፡፡
ሲጋራ ማጨስ፦ ይህን ማድረግ በከፍተኛ ሁኔታ የካንሰር ተጋላጭነትን የሚጨምር ሲሆን ከዚህ ባለፈም ሰውነት ላይ ከፍተኛ ድካምን ያስከትላል፡፡
መተኛት፦ ይህን ማድረግ ደግሞ ሆድ አካባቢ ምቾት የመንሳት እና ድካም እና ጫናን ያስከትላል።
ከዚህ ባለፈም አላስፈላጊ ውፍረትን ያስከትላል፤ ይህን ከማድረግ ከተመገቡ በኋላ ከቅርብ ጓደኛዎ ወይም ወዳጅዎ ጋር መጨዋወት መልካም ነው።
ገላን መታጠብ፦ በተመገቡበት ፍጥነት ገላን መታጠብ ምግብ ለመፍጨት የሚያስፈልገውን የሰውነት ሙቀት ሌላ ስራ እንዲሰራ ያደርገዋል፤ሰውነትን ለማሞቅ።
ይህ ደግሞ በሆድ አካባቢ ያለውን ደም ወደ ሌሎች የሰውነት ክፍሎች እንዲሰራጭ በማድረግ አንጀት ላይ ከፍተኛ ችግርን ያስከትላል።
ፍራፍሬ መመገብ፦ ለመፈጨት ቀላል ቢሆኑም ምግብ ከተመገቡ በኋላ በቅጽበት ይህን ማድረግ ግን አይመከርም።
ከቻሉ ከምግብ በፊት አንድ ሰአት ወይም ከተመገቡ ከሁለት ሰአት በኋላ፤ ያ ካልሆነ ግን መደራረብ እና መጨናነቅን በማስከተል የምግብ መፈጨትን ያዘገያሉ።
ሻይ መጠጣት፦ በተመገቡበት ቅፅበት ይህን ማድረግም አደጋ አለው፤ የምግብ መፈጨትን አስቸጋሪ በማድረግ የማስጨነቅ ስሜትን ስለሚፈጥር።
ምናልባት በፕሮቲን የበለጸገ ምግብ ተመግበው ከሆነ ደግሞ ከሻይ የሚወጣው አሲድ በከፍተኛ ሁኔታ የምግብ መፈጨቱን ስለሚያስተጓጉለው አደገኛ ይሆናል።
ከምግብ በኋላ ሻይ መጠጣት ከፍተኛ የሆነ የብረት መጠን ለሚያስፈልጋቸው ህጻናትና ሴቶች ደግሞ ጭራሽ አይመከርም።
የእግር ጉዞ ማድረግ፦ ይህን ሲያደርጉ ደግሞ ከፍተኛ የሆነ የአሲድ መጠንን በመርጨት እና የምግብ አለመፈጨትን በማስከተል ችግር ይፈጥራል።
ስለዚህም ከተመገቡ ከግማሽ ሰአት በኋላ የእግር ጉዞ ማድረግ እና በተመገቡበት ፍጥነት ይህን ማስወገድ ለጤናዎ መልካም ነው።
ምንጭ፦ mavcure.com
– See more at: http://www.fanabc.com/index.php/%E1%8C%A4%E1%8A%90%E1%8A%9B-%E1%8A%91%E1%88%AE/item/13893-%E1%8A%A8%E1%8C%88%E1%89%A0%E1%89%B3-%E1%89%A0%E1%8A%8B%E1%88%8B-%E1%8A%A5%E1%8A%90%E1%8B%9A%E1%88%85-%E1%8B%AB%E1%88%B5%E1%8B%88%E1%8C%8D%E1%8B%B1.html#sthash.asLbFMpK.dpuf